በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ 2013 የት/ዘመን የተማሪዎች ቅበላ ቅድመ ዝግጅት በተመለከተ ከሣይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር በመጡ የሥራ ኃላፊዎች አጠቃላይ ግምገማ ጥቅምት 20/ 2013 ተደረገ፡፡
የኢሲሰዩ ፕሬዚዳንት ፕ/ር ፍቅሬ ደሳለኝ ለገምጋሚ አባላቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግራቸዉን ካስተላለፉ በኋላ የኢሲሰዩ የኮቪድ 19 ወረርሽኝን በመቋቋም የተቋረጠውን ትምህርትና ስልጠና ለማስጀመር በሚቻልበት ሁኔታ የተለያዩ ስራዎች ሲሰራ ቆይቷል በዚህም ተማሪዎችን ደረጃ በደረጃ መልሶ ለመቀበል የሚያስችሉ ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች እንዲሁም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ተለይተው የስራና አፈፃፀም መመሪያ ተሰጥቶባቸዉ ለቅበላዉ የተለያዩ ዝግጅቶችም ተደርገዋል ብለዋል ፡፡