የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የ2014 ዓ.ም በልዩ የክረምት የወጣት ሲቪል ሰርቫንቶች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና መርሀ ግብር በመጀመሪያ ዙር ያሰለጠናቸውን ሁለት መቶ አስራ ሁለት ሲቪል ሰርቫንቶችን ነሐሴ 3 ቀን 2014 ዓ.ም በአባይ አዳራሽ አስመርቋል፡፡ ሰልጣኞቹም በአዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ አስራ ሶስት የፌዴራል መስሪያ ቤቶች የተወጣጡ ወጣት ሲቪል ሰርቫንቶች ሲሆኑ ለአሰራ አምስት ቀናት የተሰጠውን ስልጠናን በብቃት ማጠናቀቃቸው የተረጋገጠላቸው ሰልጣኞች ናቸው፡፡
↧